በእንተ ርእስየ

Wednesday, August 3, 2016

ዘረኝነት እና ዘረኞች

ባሁኑ ጊዜ ያለው የዘረኝነት አባዜ ከፖለቲካው አልፎ በመንፈሳዊ ቦታዎችም መስፋፋቱ ነው ይህንን የሚያራምዱ ሰዎች ደግሞ ለእግዚአብሔር እንደቀኑ አድርገው ማሰባቸው ያሳዝናል፡፡በዓለም ያሉ ደግሞ ያው ባሁኑ ጊዜ ዓለምን እንቆጣጠራታለን ብለው የሚያስቡ የእነ ኢሉሚናቲ እና መሰሎች የዘረኞች ስብስብ ድርጅት ተገዢዎች ስለ ሆኑ አይፈረድባቸውም ከእግዚአብሔር ይልቅ ሰይጣንን ስለመረጡ መጨረሻቸውም ከአጋንንት ጋር ስለሆነ ዘረኝነትን አጥብቀው ያራግቡታል ምክንያቱም ሰው ከእግዚአብሔር የሚለየው አንዱ በዘረኝነት ነውና፡፡ አመናችሁም አላመናቹሁም ዘረኞች የእግዚአብሔርን መንግስት አይወርሱም(ገላ. 5) ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን እና ቅዱሳን ቦታዎች ስፍራቸው ስላልሆነች ለክርስቶሳሳውያን ለምን አይለቁም?? ለመሆኑ ዘረኛ ማነው?? ሰውን ዘረኛ ከማለትህ በፊት ራስህን ተመልክተህ ታውቃለህ?? ይህን ካልለየህ ያልገባህ ነገር አለ ማለት ነው ወይም የዘረኝነት ምስጥሩ አልገባህም ማለት ነው፡፡ በአንተ አእምሮህ ውስጥ ሰው ሁሉ እኩል መሆኑን ካላወክ፣ሁሉንም ካልወደድክ፣የሁሉም መዳን የማያስደስትህ ከሆነ፣የሰፈርህ ሰዎች ብቻ ሰው መስለው የሚታዩህ ከሆነ፣የኔ እኔ ብቻ የምትል ከሆነ አትጠራጠር ዘረኛ ነህ፤ክርስቲያን አይደለህም፤ኢትዮጵያዊም አይደለህም፤የበግ ለምድ የለበስህ ተኩላ ነህ፡፡ ያልገባህ ምስጢር ቢኖር ትዕቢት፣ዘረኝነት እና ወዘተ የመሳሰሉ የሰው ጠባያት ለባለቤቱ የማይታወቁ መሆናቸው ነው፡፡ ለዚህ እኮ ነው ለዘረኞች የሚያስቡትም ሆነ የሚያደርጉት ነገር በሙሉ ትክክል መስሎ የሚታያቸው መቼም ቢሆን አይገባቸውም ቀኑ ከእግዚአብሔር ጋር ተቆርጣ ስትመጣ ብቻ ነው የሚገባቸው፡፡ ዘረኝነትን መዋጋት ከአጋንንት ጋር እንደ መዋጋት ስለ ሆነ ዘረኞችን መዋጋት ሐጢአት አይደለም፡፡ ምክንያቱም የዘረኞች መሪ ሰይጣን ስለ ሆነ ነው፤የሚገዙት ለሰይጣን እንጂ ለፈጣሪ አይደለምና፡፡ቅድስት ቤተ ክርስቲያንንም ሆነ ሀገርን ለዘረኞችም መስጠት ለሰይጣን እንደማስረከብ ይቆጣራልና፡፡ ባሁኑ ጊዜ ይህን ህዝብ ለመረከብ እያኮበኮበ ያለው የሰይጣን ማኅበር እንዳለ መቼም ታውቃለህ ምክንያቱም ከእውነት ይልቅ ለወሬ ቦታ ስለምትሰጥ፣ከክርስትናው ይልቅ ፖለቲካው ስለማረከህ፤ አእምሮህን ስለ ተቆጣጠረ እንዲህ አይነቱ አያመልጥህም ግን ምን ዋጋ አለው እነኚን ጊዜ ይገድባቸዋል አንተም የክርስቶስ ልጅ ሆነህ በጊዜ መገደብህ ከዚህ የሚበልጥ ኪሳራ አለ ብለ ታስባለህ??ያሳዝናል፡፡ ከሰማህ መፍትሔውን ልንገርህ?? ክርስቲያን ሁን፣ተጠመቅ፣ንስሀ ግባ፣ክርስቶስን በትክክል እወቀው፣ቅዱሳንን ምሰል (ቅዱሳን ዘረኞች አይደሉምና)፣ጸልይ፣ወደ ክርስቶስ ስጋ እና ደም ቅረብ ያን ጊዜ ውጤቱን ታየዋለህና... ወልዶ ያሳደገኝ አባቴ ይህን ነበር ያስተማረኝ ‹‹ከሁሉም ጋር በፍቅር ኑሩ ሰው በመሆኑ ብቻ ውደደው ቅረበው›› እያለ(ይህ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ካልሆነ በኔም በአባቴም ፍረዱ)