በእንተ ርእስየ

Monday, June 20, 2016

የሳጥናኤል ደብዳቤ (ማመልከቻ) ለእግዚአብሔር



ቀን፡- 22/01/7509
ቁጥር፡-666
ሁሉን ለፈጠረ ጽርሐ አርያም ለሚኖር ለእግዚአብሔር
ጽርሐ አርያም
ጉዳዩ፡- ውክልና ስለመስጠት ይሆናል
ይድረስ ለፈጣሪዬ ለእግዚአብሔር የሁሉ አስገኚ ከላይ ርዕሱ ላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት እኔ ሳጥናኤል  ከመላእክት ወገን የነበርኩ በስራዬ ምክንያት ይህም በትዕቢት አምላክ ነኝ በማለቴ አንተም ይቅር ልትለኝ እስከ ረቡዕ ድረስ ሰማይ ላይ እንዳቆየኸኝ ታስታውሳለህ፡፡ከዚያ በኋላ ለሶስት ነገድ ተከፍዬ አጋንንት፣ሰይጣን እና የአየር ጋኔን ተብዬ በትዕቢት የተነፋው ፍጡር በመሆኔ እምቢ በማለቴ ከሰማይ ጣልከኝ፡፡ በተለይ የማልረሳው በኔ ቦታ የተሾመው ሚካኤል (አቤት ስሙ ስያቃጥል ኡሁ) እሱማ ተጫወተብኝ፤ልኬን ነበር ያሳየኝ ይኸው እስከ ዛሬ ድረስ በየቀኑ እኔ የምበርዘውን ውኃ እየባረከ ህዝቡን ይጠብቃል፡፡ ከውስጤ ስለማይጠፋ ነው ከርዕሴ የሚያወጣኝ አሁን ወደ ደብዳቤዬ ኣላማ ልመልስህ፡፡ ልክ ከሰማይ እንደወደኩ ያደረኩትን መቼም አንተ ታውቃለህ አዳምን ከዚያች ገነት እንድኮበልል አደረኩ፣አንተ ላይ እንድነሳሳ፣አንተን እንዲያሳዝን፣አመጸኛ እና ወዘተ አደረኩት፡፡ ልክ እሱም እንደ እኔ ከገነት ወደ ምድር ሲመጣልኝ ጢባጥቤ ተጫወትኩበት እሱ ደግሞ ሲበዛ የዋህ ነው፡፡ ሔዋንንማ ተዋት ከባድ ናት፤ፈጣን ናት አዳም ምክሬን አልሰማ ቢል በሔዋን በኩል ስሄድበት አልቆየም ፈቃዴን ፈጸመልኝ እርቃናቸውን መሆናቸውን ገለጥኩባቸው ዕፀበለስን በልቶ ወደ እኔ ወደ ምድር መጣልኝ፣ ስምንተኛ ማዕረግ ላይ የነበረው አዳም ወደ ዜሮ መጣልኛ አቤት ደስ ስል፡፡ ከሁሉም ፍጥረት ጋር ተጣላልኝ ከመላእክት፣ከእንሰሳት (የዱር እና የቤት)፣ከአራዊት (የቤት እና የዱር)፣ከምድር ኧረ ዘርዝሬ አልጨርሰውም ቢቀር ይሻላል፡፡ የሆነበትን አንተ ታውቀው የለ እሱም ያቀዋል፡፡ ግን ምን ዋጋ አለው አንተ መጥተህ አዳንከው፣ከእጄ ማረክ፣ዋይ ዋይ ተዋረድኩ፣ተሸነፍኩ፣ጥበቤ፣ሴራዬ ባዶ ሆነ፡፡ እኔ በእባብ ስጋ ተሰውሬ ብመጣ አንተም ከድንግል ማርያም (ኡፍ! አልቻልኩም) ስጋን ነስተህ ሰው ሆነህ አዳንከው፣ወደ ቀደመ ክብሩም መለስከው ወይኔ! ወይኔ! እንደዚህ አይነት መዋረድ የለም፡፡ ሰላሳ ሶስት ዓመት በዚህ ምድር ላይ ስትመላለስ መቼ አወኩ፣ መቼ ተረዳሁህ፣ መቼ ገባኝ፣ እኔ እኮ ተራ ሰው መስለኸኝ ነበር፡፡ ይህም ሊሆን የቻለው አንተ በምታደርጋቸው ነገሮች ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ የሰው አንዳንድ ጊዜ የአምላክ ስራ ትሰራለህ ለማንኛውም ሰራህልኝ፡፡ነፍሳትን በሙሉ ማረክ ኀይሌም ደከመ፡፡
እኔም ይህን ያደረከውን ሳስብ በጣም ይቆጨኛል፡፡ ለጊዜው በዚህ ምድር ላይ ስጋ ለብስህ የተገለጥክ ጊዜ ስለምጠራጠር አንተን እንድያስወግዱ አደርግ ነበር አንዴም በሄሮድስ፣ከዝያም በደቀመዝሙርህ ልቡና (አስቆሮቱ ይሁዳ)፣በመጨራሻም በአይሁድ አሰቀልኩህ፡፡ ግን ባሰብኝ እንጂ መከራው አልቀለለልኝም፡፡ ከማኅፀን ጀምሮ እቆራኝ የነበረውን ዛሬ አልቻልኩም ይህማ ቆየ እንተ ወደዚህ ምድር ሳትመጣ ራሱ አቅቶኝ ነበር ይህም እናትህ ስትጸነስ፣ስትወለድ ከኔ ተሰውሮ የለም ወይ፡፡ ያንተንም ብተው እና ዝም ብል ይሻላል ያለወንድ ዘር በዝያ ላይ ደግሞ በድንግልና ተጸንሰህ በድንግልና ተወለድክ ኧረ ይቅር ምን እዚህ ውስጥ ከተተኝ ደግሞ፡፡ ሆኖም ግን አንተ ያደረከውን ስራ፣ያን ጊዜ የነበረኝን ስልጣን ለመመለስ ሁል ጊዜ በእቅድ እየሰራሁ ይኸው ዛሬ 2009 ዓመት ሆኖኛል፡፡ ፈጽሞ እንቅልፍ በአይኔ አይመጣም ሌሊት እና ቀን ነው የምሰራው የራሴ ኮሌጅ አለኝ በስሩ ደግሞ ብዙ ዲፓርትመንቶች (ትምህርት ክፍሎች) አሉ፡፡ ትምህርት ክፍሎች ግን በጣም ብዙ ናቸው ለምሳሌ ምንፍቅና፣ተሀዲሶ፣አህዛብነት፣አስማት፣ሟርት፣ጥንቆላ፣ዝሙት፣ዘፈን፣…. ኧረ ይቅር ብዛቱን እኔ ራሴ ዘርዝሬ አልጨርሰውም፡፡ለአዳም ልጆች ይህ ሁሉ የተለያየ ይመስላቸዋል ነገር ግን የሁሉም ዲፓርትመንቶች ዲናቸው እኔ ነኝ ሁሉንም እቆጣጠራቸዋለሁ የማይሰራውን ሰነፍ ሰራዊት በጭካኔ መንፈስ እቀጠቃለሁ ስልጣን ሰጥተኸኝ የለ፡፡ ህዝቡን ለማወናበድ ስል ትምህርት ክፍሎችን የተለያዩ አስመስላቸዋለሁ ዓላማቸው ግን አንተ እንደሚታውቀው የአዳምን ልጆች ካንተ እጅ አውጥቶ በሲዖል ማኖር ከዚያም በኋለኛው ዘመን ለገሃነም ማሰረከብ ነው፡፡ ዛሬ ዛሬማ የራሴ ቤተመቅደስ እንዳለኝ አንተ ታውቃለህ አንተን የማያውቁ በእውቀት ብቻ የሚነዱ፣ እንጅነር ቅጣው እጅጉ ከተለያትማ ራስዋን የሳተች አሜሪካ እኮ ናት ቤተ መቅደሴን የሰራችልኝ፡፡ አንዱ አዋቂ ነኝ ባይ አንቶንሌቪ በሳንፍራንሲስኮ ውስጥ የራሴ ቤተመቅደስ ሰርቶልኛል፡፡ ስጋ ባይኖረኝም ስጋዬን ይበላሉ፣ደም ባይኖረኝም ደሜን ይጠጣሉ ልክ ያንተ ትክክለኛው ስጋ እና ደም እንደሚበላ እና እንደሚጠጣ፡፡ በየጊዜው መስዋዕት ይሳውልኛል የሚሰዋው ደግሞ የሕጻናት ደም ነው ያን ጊዜ በስጋ ወደዚህች ዓለም መጥተህ የነበረ ጊዜ ገና በስጋ የሁለት ዓመት ሕጻን ሆነህ ሳለህ በሄሮድስ አድሬ ላሰገድልህ ነበር ምክንያቱም አምላክ መሆንህ መች አውቄ እኔ የመሰለኝ ታላቅ ነብይ፣ንጉስ ወይም በዝያን ጊዜ ካሉት ነገስታት ያለቅህ እንደምትሆን ብቻ ነበር እንዲህ አስቤ ነው ያን ጊዜ እነኛን ሁሉ ሕጻናት ያስገደልኩት፡፡ ዛሬም የሐጻናት ደም በየቦታው ይፈሳል በተለይ በመቅደሴ እና በማኅበሬ ዘወትር የሰው ደም ይፈሳል በተለይ የሕጻናት፡፡ አንተ ንጹህ መስዋዕት ትወድ የለ እኔም የንጹሐን ሕጻናትን ደም እወዳለሁ፡፡ ትልቅ ማኅበር እንዳለኝም ታውቃለህ ይህም ኢሉሚናቲ ይባላል፡፡ በጣም የምኮራበት ማኅበር ነው ምክንያቱም የማይገባበት ቦታ የለም ገንዘብ ላይ፣ህክምና ውስጥ፣ባሕል ውስጥ፣ ኧረ አሁንማ በቤትህም ገብቷል ልክ አንተ ዮሐንስ ባለ ራዕዩን እንዳናገርከው በራዕይ ዮሐንስ ምዕራፍ 12፣13 ሌላም፡፡ ተሀድሶ እያሉ ቤትህን ያውካሉ፣ጥርጣሬን፣ክህደትን እና አመጽ በቤትህ ሞልተዋል፡፡ ስለ እኔ ማንነት የሚያጋልጡ መጻሕፍትን ስያጣጥሉ እያየኻቸው ነው አይደል ለምሳሌ መጽሐፈ ሄኖክ- የኔ ማንነት እኮ የተጋለጠው በሱ ነው፡፡ ዛሬ ያሉ መናፍቃን እና ተሀዲሶዎች በአደባባይ የሚቃወሙት ይህን መጽሐፍ ነው ብልጦቹ የኔ ወደጆች እንደ አሜሪካ፣እንግሊዝ-እንግላንድ (አንጀል ላንድ)፣ሌሎችም ሀገሮች መጽሀፉን በተለየ መልኩ ይፈልጉታል፡፡ ምክንያቱም እኔን ስለሚከተሉ ሌሎች ሰዎችም ወደነሱ እንዲመጡ ከዚያ የኔ እንዲሆኑ ይፈልጋሉ፡፡ ያቺን ሀገር ማለቴ ኢትዮጵያ ዛሬ የዘረኞች መነኻሪያ የሆነች መልኳን የቀየረች ምድር እንኳን የመጽሐፈ ሄኖክ መገኛ የነበረች ሀገር ዛሬ መጽሐፉን አጥብቃ ትቃወማለች ምክንያቱም ካንተ ይልቅ እኔን መስማት ጀምራለችና ካንተ በረከት ይልቅ የኔን የጥንቆላ ስራ፣አስማት እና ሴራዎች ላይ የሚደገፉ ሰዎች የበዙባት ሀገር ሆናለች፡፡ ይገርመሃል የኔ ወደጅ የነበረች የእንግሊዝ ንግስት የነበረች ንግስት ኤልሳቤጥ ጄምስ ብሩስ የሚባለውን ሰው ወደ ኢትዮጵያ ልካ አስራ ሰባት ዓመት በዝያች ሀገር እንዲኖር አድርጋ፣ የሀገሩን ቋንቋ ተምሮ፣ ከባህሉ ጋር ተለማምዶ የሀገሩ ህዝብ ደግሞ ሞኝ አትለው የዋህ እንግዳ መቀበል በሚባል አባዜ ከውጪ የሚመጡ እንግዶችን ማንነታቸውን ሳያጠኑ እስከ ቤታቸው ድረስ ያዘልቃሉና ይህ ሰውም ጎንደር በሚገኘው ሙዚየም ከገዢው አካል ጋር በመወዳጀት፣በመቅረብ፣በመላመድ መጽሐፈ ሄኖክን ሰረቆላት ሄዶ አስረከባት፡፡ ይህን ያደረገችበት ምክንያት የኢትዮጵያ ሕዝብ ስለኔ እንዳያውቅ እና በመጨረሻው ዘመን የኔ አምላኪ እንዲሆን ነበር፡፡ ይህ እውነትም አንተ ለሀገሪቱ ያለህ ቃል ኪዳን፣የቅዱሳን ምልጃ፣የእናትህ ጸሎት እና የአንዳንድ በጎ ሰዎች ጸሎት ነው የሚያቃጥለኝ እንጂ ተሳክቷል ማለት እችላለሁ፡፡ ብዙዎች የዚህ መጽሐፍ ተቃዋሚ ሆነዋል፡፡ የሚገርመው ግን አለ ማስተዋላቸው ነው መጽሀፈ ሄኖክ ስለ እኔ ብቻ አይደለም የኔን ትምህርትም የሚያጋልጥ ነው ይህም የሳይንስን ትምህርት የሚያዋርድ ስለ ሆነ እኔ የሚፈልገው ወደጆቼም የሚፈልጉት ሰው ከሃይማኖት ትምህርት ይልቅ የሳይንስን እንዲቀበል ለማድረግ ነው፡፡ በአጠቃላይ መጽሐፈ ሄኖክን አጥብቄ ስለሚጠላው ነገርኩህ እንጂ ዛሬ መናፍቃንም ሆኑ አስመሳዮቹ ተሀዲሶች የሚቃወሙት መጻሕፍት ሁሉም ያንተን መንገድ የሚያሳዩ የኔን መንገድ የሚያጋልጡ ስለ ሆኑ የኔ ወደጆች አይፈልጉትም፡፡ ዛሬ በቤትህ ተጣብቀው ያሉ ተሀድሶ መዥገሮች መጨረሻቻው አኔን ወደ ማምለክ ነው ምንም ማረጋገጫ አያስፈልግም ልክ በውጪ ያሉ መናፍቃን እንድሚያደርጉት ናቸው ልዩነታቸው ውስጥ በመሆናቸው ብቻ ነው፡፡ እንግዲህ እንዳልኩህ ይህ ኢሉሚናቲ ትልቅ ስራ እየሰራ ነው ብዙ ዓመት የስራ ልምድ አለው፡፡ብዙ አገልግሎት እየሰጠ ነው ከዚህም ውስጥ አልባሳትን፣መድኃኒቶችን፣ምግቦችን፣መጠጦችን ወዘተ ለዓለም ያከፋፍላል፡፡ በምርቱ ላይ ደግሞ የኔን ዓላማ ያራምዳል አሳረፈኝ እያልኩህ! ይህን ማኅበር ብዙዎቹ ቶሎ አይረዱትም፣የተረዱት ደግሞ ቶሎ ይገደላሉ፡፡ እንዳልነግርህ አንተ ሁሉን አዋቂ ነህ፡፡ ከዚህ ማኅበር ወጥተው፣ተለይተው፣ተቃውመው ላንተ የሰገዱ ይገደላሉ ባጠቃላይ አንተን የሚያመልኩ ክርስቲያኖች በዚህ ማኅበር አይወደዱም እደ እንቅፋት ይቆጠራሉ ሁል ጊዜ ይታረዳሉ፣ይገደላሉ ቦታም የላቸውም፡፡ይህን ማኅበር የተቀላቀሉ ደግሞ በዓለም ላይ ልዩ ትኩረት የተሰጣቸው ባለስልጣናት፣ባለሀብቶች፣ዘፋኞች፣የካቶሊክ እምነት ጳጳስንም ጨምሮ ሌሎችም የዚጅ ማኅበር አባል ናቸው፡፡ወነኛው የዚህ ማኅበር ምልክት ደግሞ 666 ነው ለዚህ ነው ለደብዳቤዬ ልዩ ቁጥሩ 666 ያደረኩት፡፡ እስቲ በዓለም ላይ ያሉ ዓለም ዐቀፍ አርማዎችን ተመልከት በተለይ አደግን የሚሉ ሀገሮችን እያንዳንዳቸው ከኔ ዓላማ ጋር የተገናኙ ናቸው ማላቴ ኩራቴ የሆነው የኢሉሚናቲ ማኅበር አርማ ማለቴ ነው፡፡ አሁንማ ይባስ ብለው የኔ መንፈስ የሚሰርጽበትን ቴክኖሎጂ አሰርቻለሁ ይህም ማይክሮ ቺፕ ነው፡፡ አንተ ግን ቀድመህ ዮሐንስ በራዕይ እንዲመለከት አደረግህ ይም በምዕራፍ 13 ላይ ያለው፡፡ ለማደናበር ያህል ቴክኖሎጂው ያስፈለገበት ምክንያት የዓለም አሸባሪዎችን ለመቆጣጠር እና ለሰው ደኅንነት ነው ብዬ አስለፍፋለሁ፡፡ ለመሆኑ አሸባሪዎች እና የሰውን ደኅንነት የነሱ ማናቸው ራሰቸው አይደሉም እንዴ፡፡ አንዳንዴ እኔ ከማሰራቸው ውጪ እኔ የሚያስቡት ተንኮል እና ክፋት ይገርመኛል ወይ የአዳም ልጆች!
ለመግለጽ እንደሞከርኩት አሁን ስራዬን የሚሰራልኝ ዓለም ራሱ ነው፡፡በሕግህ የተከለከለውን ያደርጋሉ፣ያን ጊዜ የሰዶም እና የጋሞራ ሕዝብ አጥፍተህ ሎጥ እና ቤተሰቦቹን ብቻ እንዳዳንክ እያወቁ ዛሬ ላይ ሰዎች ደግሞ ይፈቀድልን እያሉ እኮ ነው፡፡እውነት ይህ እኔን ራሱ ያስቀኛል ምክንያቱም ሰዶም እና ጋሞራ የጠፉበትን ተግባር እና ድርጊት ይፈቀድልን ብሎ መነሳት ምንኛ ጥፋት፣ሞኝነት፣አለዋቂነት እና ድንቁርና ነው የሚገርመው ደግሞ በዚህ ምድራዊ እውቀት የመጠቁ ናቸው ይህን ስራ የጀመሩት፡፡ ምን ያድርጉ እውቀት እንጂ መች ጥበብ አላቸውና፡፡ ዳንኤል በትንቢቱ በምእራፍ 12 ‹‹በመጨረሻው ዘመን እውቀት ይበዛል›› ስለሚል ይህ ይፈጸም ዘንድ ሆኖአል፡፡ ዳንኤልም እውቀት ይበዛል አለ እንጂ ጥበብ ይበዛል አላለም፡፡ ጥበብ ቢሆንማ ኖሮ አንተን በፈሩ፣ባከበሩ፣በተገዙልህ፣ባመለኩ፣ባወቁህ ነበር፡፡ አሁንማ ሳየው እኔ ያልሰራሁትን ስራ እየሰሩ ናቸው፡፡ ከኔ የሚበልጥ ጥበብ ያለቸው እስኪመስለኝ ድረስ፡፡
በአሁኑ ጊዜ ያለው ጭካኔ ይገርማል መለያየቱ፤ዘረኝነቱ፣መገዳደሉ፣ጠቡ፣ክርክሩ፣ትዕቢቱ፣ክፋቱ፣ሙስናው፣የሀገር ፍቅር ማጣት፣አለባበሱ፣ ኧረ ስንቱን ልንገርህ በቃ ምን ልበልህ ጰውሎስ ለጢሞተተዎስ በሁለተኛ መልእክቱ የጻፈው በምዕራፍ ሦስት ከቁጥር አንድ እስከ አስር ድረስ ያለውን በሙሉ የሚፈጽም ሰው ነው ያለው፡፡ ያን ቃል እንድፈጽሙ እኔ የተወሰነ ነገር ነው የምሰራው ራሳቸው ናቸው የሚገፋፉኝ፣የሚነካኩኝ፣እኔ ያላሰብኩትን ሀሳብ እያሳሰቡኝ የኔን ቦታ ወስደው በራሳቸው ሰይጣን ሆነዋል ፡፡ ጠዋት ቤትህ ይመጣሉ ሌሊት ደግሞ ርኩስ መንፈስን በወደጆቹ የሚልኩ የሚያስልኩ ሰዎች የበዙበት ጊዜ እኮ ነው እኔ ደግሞ እነዚህን የተላኩ መናፍስት ስራቸውን መስራታቸውን እና አለመስራታቸውን ለመቆጣጠር ብዙ ጊዜ ይወስድብኛል፡፡ ሰራዊቴ ተግባራቸው በትክክል ካልተወጡ እነሱን እየቀጣሁ በሰራዊቴ ዘንድ ጨካኝ ተብያለሁ፡፡ እና ያሉት ያደጉ ሀገሮች የሚባሉት እኮ ላንተ የተገዙ ሳይሆን ለኔ የተገዙ ናቸው፡፡ አሜሪካን ተመልክተሃታል መላ ሁኔታዋ እኮ የኔ፣ለኔ ናት፡፡ እስኪ የአሜሪካን ዋና ከተማ ዋሽንግተን ዲሲን ከላይ ሁነህ ተመልከታት በድሮ ዘመን ትመለክ የነበረችዋን ወፍ እኮ ነው የምትመስለው፡፡ በዶላራቸው ላይ ተመልከት እሺ እኔ ምን ላድርግ በዚህ እኔ መጠየቅ አለብኝ በፍጹም አይሆንም፡፡ ከላይ በገለጥኩት ትምህርት ክፍሎች ስር በሰፊው እየሰራ፣ብዙ ተማሪ እየተቀበለ ያለው የዘፈን ትምህርት ክፍል ነው፡፡ አሁን በቅርቡ ባቀረበልኝ ማመልከቻ መሠረት እራሴን ችዬ ኮሌጅ ወይም እንስትቲዩት ካልሆንኩ ብሏል፡፡ በርግጥ እየሰፋ በመምጣቱ እንደ ዝሙት እራሱን ችሎ መገንጠሉ አይቀርም በቅርቡ የትምህርት መመሪያውን (ካርኩለም) ልኮልኛል፡፡ ስመለከተው የሚያስኬድ ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም በሁሉም ሀገሮች ይህ የሙዚቃ እንዱስትሪ እየሰፋ መጥቷል ያቺ ሀገር ቃል የገባህላት ሀገር ኢትዮጵያ ሳትቀር ይህን እንዱስትሪ በስፋት እያስፋፋች ነው፡፡ በቅርቡ እንኩዋን ታለንት ሾው እያለች ልጆችዋን ታወዳድራለች፤ህዝቡዋ ደግሞ የዋህ ስለሆነ እንጄራ የወጣለቸው ስለሚመስላቸው ይቦንሱታል፣መልካቸውን አጥተዋል፣ባሪያ ሆነዋል፤ወይ የድንግል ማርያም ልጆች፣የቅዱስ ያሬድ ልጆች፣ኧረ ስንቱን ልንገርህ ዛሬ ያሉ የኢትዮጵያ ልጆች ግን የኤርምያስን ቃል (ትንቢት) የጣሱ ይመስለኛል፡፡ ኢትዮጵያን ያነሳውልህ በጣም ስለምታቃጥለኝ ነው ጸሎት እኮ አይቋረጥባትም በገዳም ብትሄድ ሁል ጊዜ ጸሎት ነው ዛሬ ዛሬ ግን መስለው የሚገቡ ቢኖሩም እንጂ፣ ጠዋት ኪዳን ከዝያም ቅዳሴ አይቋረጥባትም  ይህ ነው የሚያንገበግበኝ፡፡እና ይህ የሙዚቃ እንዱስትሪ በመስፋፋቱ የተነሳ ባሉ ክልሎች፣ባሉ ቋንቋዎች በሙሉ የራሳቸው የውድድር መድረክ አላቸው፡፡ ለምሳሌ በአማራ ክልል ባላገሩ፣በአሮሚያ ክልል ደደራሮ ወይም ታለንት ሾው በሚል ያወዳድራሉ ከዚያም ተወዳዳሪዎቹ በዓለም ዘንድ ታዋቂ ይሆናሉ፡፡ ከዚህ የተነሳ በዚያች ሀገርም ሆነ በዓም አቀፍ የሙዚቃ ቤቶች የበዙበት፣ዳንስ ቤቶች፣የማታ ክበብ (ናይት ክለብ) እያሉ የብዙ ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል በተለይ የወጣት ሴቶች እና ወንዶች የተበላሸበት ዘመን ነው፡፡ እነኚ የሙዚቃ እና ዘፈን ቤቶች ደግሞ ብቻቸውን አይደሉም በመጠጥ ይታጀባሉ ከዚያ በኋላ የሚመጣውን ታውቃለህ ዝሙት፣በሽታ - ክፉ ኃጢአታ ከዚያ ካንተ መለየት ይሆናል፡፡ እስኪ የሚለጠፉ ትላልቅ ማስታወቂያዎችን ተመልከት በዚያች ሀገርም ሆነ በሌላው ዓለም የመጠጥ ማስታወቂያ፣የፋሽን እና ከሀገሪቱ ማንነት ጋር የማይሄድ ነገር ነው፡፡አንተ ታውቀዋለህ ዛሬ የዓለም ዕውቅና ለማግኘት ያንተ መሆን ሳይሆን የኔ መሆን ብቻ ነው የሚያዋጣው፡፡ ሙዚቀኞችን አይተሃቸዋል የኔ እኮ ናቸው ብዙዎች ነፍሳቸውን ለኔ ሽጠዋል፡፡ ከዚያ የሚፈልጉትን ብር፣ገንዘብ እሰጣቸዋለሁ፡፡ ገንዘብ ካገኙ ደግሞ አንተን አይፈልጉም፡፡ በቃ ምን ልበልህ የኔን ስራ እየሰሩልኝ ስለ ሆነ፣እኔ የማስበውን ሳይሆን እኔ ያላሰብኩትን ስለሚያስቡ፣እኔ ያለደረኩትን ስለሚያደርጉ ከአሁን በኋላ መጠየቅ የለብኝም ራሳቸው ይጠየቁ እንጂ፡፡ ብዙውን ለማውራት በጣም ጊዜ ያጥረኛል ምክንያቱም የፈጠርካቸው ሰዎች የሚሰሩትን ስራ፣የሚያስቡትን ሀሳብ፣የሚተገብሩትን ተግባር፣ ወዘተ ኦዲት ስለማደርግ ነው የሄደው፡፡ በፊት ስራዬን ላሰራቸው ነበር የምሄደው አሁን ግን ስራቸውን ኦዲት ለማድረግ፣ በክብር መዝገብ ለመመዝገብ፣ስራቸውን ለማድነቅ እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡ስለዚህ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በእኔ ቦታ ሆነው አኔ እስከምነግርህ ድረስ እንዲሰሩ የወከልኳቸው መሆኔን አሳስባለሁ፡፡እንግዲህ ፈጣሪዬ ይህን ደብዳቤ መጻፍ የቻልኩት ስራቸው ስለሚገርመኝ ነው ባንተ ዘንድ አይደለም በሰራዊቴ ዘንድ የሚጠሉ ሰዎች የበዙበት ዘመን ነው፡፡ እንኚ የውሸት አጥማቂዎች የሚሰሩትን ትርዒት ተመልክተሃል እነዚ ሰይጣንን ወደ ሰው የሚልኩ እና የሚያስልኩ እኮ በኔ ዘንድ እንጂ በሰራዊቴ ዘንድ አይወደዱም እናም ብዙ ነገሮችን ስመለከት ይህን ደብዳቤ ለመጻፍ አነሳሳኝ፡፡ ሌላ ደብዳቤ ጽፌ ወይም በአካል በሌላ ክስ እስከሚመጣ ድረስ...፡፡
setan symbol.jpgየሀሳት አባ~
666
ሳጥናኤል ከምድረ ሲዖል

No comments:

Post a Comment